image
image
image
image
image

በልደታ ክፍለ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያው 6 ወር ውጤታማ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ተቋማት እውቅና ሰጠ።

የካቲት 14, 2017
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው 6 ወር የተሻለ የስራ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማትና ሰራተኞች እውቅናና ሽልማት ተበርክቷል። የጽ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሮ ዘነበች ኢረና የህብረተሰቡን የአገልግሎት ፍላጎት ለማርካት ያከናወናቸው ተግባራት ውጤታማ እንደነበሩ ገልጸው የነበሩ ጥንካሬዎችን በማጠናከርና ክፍተቶችን በመሙላት በቀጣይ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ በመተባበር ልንሰራ ይገባል ብለዋል። በሲቪል ምዝገባና ነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት የሚሰጡ አገልግሎቶች እየተሻሻሉ መምጣታቸውንም ገልጸዋል። ለህብረተሰቡ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማሻሻልና የህብረተሰቡን እርካታ ለማሳደግ በተቀመጠው ስታንዳርድ መሠረት አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑንም ገልፀዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች