ዜና | Oduu | News
የልደታ ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት አገልግሎቱን በማዘመን ደንበኞቹን በቅልጥፍና እያስተናገደ ይገኛል።

የልደታ ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት አገልግሎቱን በማዘመን ደንበኞቹን በቅልጥፍና እያስተናገደ ይገኛል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያው 6 ወር ውጤታማ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ተቋማት እውቅና ሰጠ።

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው 6 ወር የተሻለ የስራ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማትና ሰራተኞች እውቅናና ሽልማት ተበርክቷል። የጽ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሮ ዘነበች ኢረና የህብረተሰቡን የአገልግሎት ፍላጎት ለማርካት ያከናወናቸው ተግባራት ውጤታማ እንደነበሩ ገልጸው የነበሩ ጥንካሬዎችን በማጠናከርና ክፍተቶችን በመሙላት በቀጣይ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ በመተባበር ልንሰራ ይገባል ብለዋል። በሲቪል ምዝገባና ነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት የሚሰጡ አገልግሎቶች እየተሻሻሉ መምጣታቸውንም ገልጸዋል። ለህብረተሰቡ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማሻሻልና የህብረተሰቡን እርካታ ለማሳደግ በተቀመጠው ስታንዳርድ መሠረት አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑንም ገልፀዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን የልደታ ክ/ከተማ የሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት ገለጸ።

ጽ/ቤቱ ከተለያዩ ጽ/ቤቶች ጋር በቅንጅት የተሰሩ ስራዎችን ገምግሟል ። የጽ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሮ መቅደስ ያደታ እንደገለጹት ከተለያዩ ጽ/ቤቶች ጋር ቅንጅታዊ አሰራርን በመፍጠር በጋራ በመስራት የተቋሙን ሰፊ ስራዎች ቀልጣፋ እንዲሆን ስለሚረዳ በትስስር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። ኃላፊዋ አክለውም በተቋሙ የሚሰጠውን አገልግሎት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንሰራለን ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ውጤታማ ስራ ለመስጠት በቅንጅትና በትስስር መስራት አስፈላጊ በመሆኑ በጋራ እንሰራለን ብለዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
የወሳኝ ኩነት ምዝገባን በወቅቱ በማስመዝገብ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነታቸዉን እንዲያረጋግጡ ለ300 ለሴቶች ስልጠና ተሰጠ።

የልደታ ክፍለ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ መቅደስ ያደታ እንደተናገሩት ሴቶች በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ ተጠቃሚነታቸዉን ለማረጋገጥ የወቅታዊ ኩነት ምዝገባ ወሳኝ መሰረት መሆኑን በመግለፅ የሚወለድ ህፃናት በወቅቱ የልደት ካርድ እዲያወጡ በማስቻል የህፃኑን ማንነት እዲረጋገጥ በማድረግ ሴቶች ማህበራዊ ግዴታችሁን መወጣት ይገባችኋል በማለት ገልፀዋል። ወ/ሮ መቅደስ አያይዘው ሴቶችን ማብቃት ሀገራዊ እድገትን ያሳልጣል፣ ሴትን ማብቃት ሀገርን ትውልድን ማነፅ በመሆኑ ሴቶች በማስተማር ያላቸውን ሚና ማሳደግ ያስፈልጋል በማለት ሴቶች በጽ/ቤታችን እያደረጉ ያለው አስተዋፅኦ የሚበረታታ መሆኑን በመግለፅ ይበልጥ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ሲሉ ተናግረዋል። ተሳታዎችም ሴቶችን ለማብቃት ታስቦ በዚህ ልክ መድረክ በማዘጋጀት ግንዛቤ መሰጠቱ የተሻለ ነው በማለት አንስተዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
የተቋም ግንባታ ሂደታችን ግቡን እዲመታና አገልግሎት አሰጣጡን ለማቀላጠፍ የዘርፉን ባለሞያ ማብቃት የግድ መሆኑን ተጠቆመ።

የልደታ ክፍለ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት በርካታ የህዝብ ክፍሎችን እንዲሁም ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን የሚሰጥ ተቋም ሲሆን የተቋም ግንባታ ሂደቱና አገልግሎት አሰጣጡን የተሻለ ለማድረግ ለአጠቃላይ የተቋሙ አመራርና ባለሞያዋች ስልጠና ተሰቷል በስልጠናዉ ላይ ንግግር ያደረጉት የልደታ ክፍለ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ መቅደስ ያደታ ይህ ስልጠና የተቋማችንን የአገልግሎት አሰጣጡንና ከተገልጋዮ ጋር የምናደርገዉን ተግባቦት ላቅ ያለ ደረጃ የሚያሸጋግር በመሆኑ ጠቃሚና ለተቋማችን ትልቅ ሚና ያለዉ ስልጠና ነዉ በማለት ገልፀዋል:: ሰልጣኞችም ስልጠናው በምንሰጠው አገልግሎት ላይ ውጤታማ እንድንሆን የሚያደርገ ነው በማለት አንስተዋል

image
image
image
image