በመሆኑም ኤጀንሲው የወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና የብሔራዊ መታወቂያ አዋጅ 760/2004 ዓ.ም እና በተሻሻለው አዋጅ 1049/2009 ዓ.ም እንዲሁም የአዲስ አባባ ከተማ አስተዳደር አስፈጻሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣ ማሻሻያ አዋጅ 84/2016 በተጨማሪም በነዋሪነት አገልግሎት መመሪያ ቁጥር 145/2015 መሰረት በማድረግ ልደት፣ ጋብቻ፣ ፍቺ፣ ሞት፣ አባትነትን በፍርድ ቤት መቀበል፣ ልጅነትን በፍርድ ቤት መቀበል እንዲሁም የነዋሪነት አገልግሎቶችን ማለትም የነዋሪነት መታወቂያ፣ ያላገባ፣ የነዋሪነት፣ መሸኛ፣ የነዋሪነት ማረጋገጫ፣ በህይወት ስለመኖር፣ ለማህበራዊ ዋስትና የእናትነት፣ የአባትነት፣የልጅነት እህትነት፣ ወንድምነትና አያትነት ከቅጽላይ በማየት የማረጋገጥ እና ለማህበራዊ ዋስትና ብቻ ያላገባ ማስረጃ በደብዳቤ የመስጠት አገልግሎቶች ይሰጣሉ፡፡ በመሆኑም ተቋሙ አገልግሎት ሰጪ ተቋም እንደመሆኑ መጠን የተቋሙን ራዕይና ተልዕኮን ከግብ ለማድረስ ዜጎች የሚፈልጉትን አገልግሎት ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት አሰራር ስርዓት በመዘርጋትለዜጎች አገልግሎቶች የሚሰጥባቸውን ቦታ፣ የአገልግሎት ቅድመ ሁኔታና ደጋፊ ማስረጃዎች ስታንዳርድ(ጊዜና ጥራት) በግልጽ በማስቀመጥ በተቋሙ እና በዜጎች መካከል ባለው የአሰራር ሂደት ላይ መብትና ግዴታቸውን እንዲረዱ እና የአገልግሎት አሰጣጡን ፈጣንና ቀልጣፋ በማድረግ የዜጎችን የእርካታ ደረጃ ከፍ ማድረግ ያስችላል፡፡