የክፍለ ከተማው ሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት ተግባርና ሃላፊነት
- የኤጀንሲዉን ህግ እና ለስራ የሚያግዙ አሰራሮችን መፈጸም እና ማስፈጸም፣ በተገቢዉ አደራጅቶ መያዝ እንዲሁም በወረዳ በአግባቡ መፈፀማቸዉን መከታተል፣
- ነዋሪዎች በምዝገባም ሆነ በሌሎች የነዋሪነት አገልግሎቶች ጥያቄ ለማቅረብ የሚችለበትን ቅድመ ሁኔታ በተገቢዉ ቦታ ማስቀመጥ፣ ግንዛቤ መፍጠር እንዲሁም ለአገልግሎት ቅልጥፍና የተዘጋጁ ፎርሞችን አባዝቶ ማቅረብ፤
- በኤጀንሲው እየታተሙ የሚሰራጩትን ለተቋሙ አገልግሎቶች አስፈላጊ የሆኑ ቅጾችን፣ ካርዶችን፣ ሰርተፍኬቶችን እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ሰነዶችን በንብረት አስተዳደር አሰራር ከኤጀንሲዉ በመረከብ በስራ ሊይ እንዲውሉ ለወረዳዎች ማሰራጨት እንዲሁም በአግባቡ በስራ ሊይ መዋላቸዉን መከታተል እና መቆጣጠር፤
- የዲጂታል መታወቂያን የማተም እና የማሰራጨት፤
- ለአገልግሎት አሰጣጡ ተገቢው እና አስፈሊጊዉ የሰው ሃይል መኖሩን በማረጋገጥ ክፍተት ሲኖር ከወረዳዎች በሚቀርበው መሰረት ለሚመለከተዉ አካል እንዲሟላ ጥያቄ ማቅረብና ተከታትሎ ማስፈፀም፤
- የኤጀንሲዉ የቴክኖሎጂ ሃብቶችን በጥንቃቄ መምራት፣ ደህንነቱን ማረጋገጥ እንዲሁም ከአቅም በላይ የሆነ ብልሽት ሲኖር ለኤጀንሲዉ ማሳወቅና ደህንነቱን መከታተል፣
- ለአገልግሎት አሰጣጡ አስፈሊጊውን የሰው ሃይል እንዲሟላ ለሚመለከተው አካል ጥያቄ ማቅረብ፣ የሰዉ ሃይልን ማሰልጠን፣ ማብቃት እና አሰራርን ተላላፎ የተገኘ ሰራተኛ ሲኖር ተጠያቂ እንዲሆን ማድረግ ተከታትሎም ማስፈጸም፤
- ከዚህ መመሪያ ውጪ የሆነ ማንኛዉም ህገ-ወጥ ተግባር ሲፈጸም ተከታትሎ ህጋዊ እርምጃ መውሰድና እንዲወሰድ በማድረግ ለክፍለ ከተማውና ለኤጀንሲው ሪፖርት ማድረግ፤
- የተቋሙን የሰራተኛ የደንብ ልብስ አጠቃቀም ተፈጻሚነቱን መቆጣጠር፤
- በክ/ከተማ እና በወረዳ ደረጃ የተከናወኑ ተግባራትን በመጠመር ለኤጀንሲዉ ወቅታዊ ሪፖርት በየጊዜዉ ማቅረብ፡፡